ምክኒያቶቹ ምንድን ናቸው?

10
ባሕር ዳር: ሰኔ 02/2018 ዓ.ም (አሚኮ) በሕጻናት ላይ የሚፈጸሙ የሳይበር ጥቃቶች ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደጉ ነው።
ምክኒያቶቹ ምንድን ናቸው?
✍️የወላጆች የዲጂታል ዕውቀት ክፍተት (Digital Literacy Gap)
በኢትዮጵያ 80 በመቶ ወላጆች ልጆቻቸው ኢንተርኔት ላይ ምን እንደሚሠሩ አንደማያውቁ ጥናቶች ማረጋገጣቸውን የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አሥተዳደር መረጃ ያሳያል።
ይህ ክፍተት ልጆችን ለሳይበር አዳኞች የተመቹ ያደርጋል።
✍️ማግለል
ማኅበረሰቡ ተጎጂዎችን የመውቀስ (Victim-blaming) ዝንባሌ ልጆች ስቃያቸውን በውስጣቸው አፍነው እንዲቀሩ እና የደረሰባቸውን ጥቃት በግልጽ ወጥተው እንዳይናገሩ ያደርጋል።
✍️ያለገደብ የሚሰጥ ነፃነት
ሰፊ የኢንተርኔት ተደራሽነት እና የታዳጊዎች ከፍተኛ ፍላጎት ያላንዳች የደህንነት ገደብ ሲገናኝ፣ ልጆች አደገኛ የኦንላይን ባህሪያትን (ለምሳሌ የግል መረጃን ማጋራት) እንዲላመዱ ያደርጋቸዋል።
💪እንዴት እንጠብቃቸው?
#የዲጂታል ቁጥጥር (Parental Controls) ማድረግ
-በወላጆች ወይም በልጆች ስልክ ላይ የደህንነት ማስተካከያዎችን (እንደ Google Family Link, YouTube Kids) መጫን
-የማኅበራዊ ሚዲያ የግላዊነት ማስተካከያዎችን (Privacy Settings) በማስተካከል የልጆችን መረጃ “Private” ማድረግ
• አጥቂዎች እንዳይከታተሏቸው የስልካቸውን የቦታ መረጃ ማሳያ (Location services) ማጥፋት
#ግልጽ የውይይት ባሕልን ማሳደግ
-ኦንላይን ላይ የሚያስፈራ ነገር ካጋጠማቸው ሳይፈሩ እንዲናገሩ ግልጽነት የተሞላበት የቤተሰብ ድባብ መፍጠር።
#የሕፃናትን የዲጂታል ንቃት ማሳደግ
-ለማያውቁት ሰው የጓደኝነት ጥያቄ (Friend request) እንዳይቀበሉ ማስገንዘብ
• የይለፍ ቃል (Password)፣ ፎቶ፣ እና የግል መረጃን ለማንም እንዳያጋሩ ማሳሰብ
የአሚኮ ዲጅታል ቤተሰብ ይሁኑ!
ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!
Previous articleበዘንድሮው ክረምት 25 ሚሊዮን የፍራፍሬ እና የቡና ችግኝ በክልሉ ሁሉም አካባቢ ይተከላል።
Next articleየሚኒስትሮች ምክር ቤት የ2019 በጀትን ጨምሮ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ ውሳኔ አሳለፈ።