“መብቴን ተጠቅሜ መምረጤ ለሀገሬ ያለኝን ፍቅር ማሣያ ነው” አካል ጉዳተኛው መራጭ

8
🇪🇹🗳️ጎንደር፡ግንቦት 24/2018 ዓ.ም (አሚኮ) የጎንደር ከተማ ነዋሪዎች ድምጻቸውን እየሰጡ ነው። በምርጫው አካል ጉዳተኞችም እየተሳተፉ ነው።
ከአሚኮ ጋር ቆይታ ያደረጉት አቶ ሙሉጌታ አባተ ሀገር ከፍ እንድትል እና ዴሞክራሲ እንዲጎለብት ድምጻቸውን መስጠታቸውን ተናግረዋል።
‎‎የ72 ዓመቱ አቶ ሙሉጌታ ባለፉት ስድስት ምርጫዎች መሳተፋቸውን አስታውሰዋል። በሰባተኛው ጠቅላላ
ምርጫም ድምጻቸውን መስጠታቸውን ገልጸዋል።
‎የድምጽ አሰጣጥ ሂደቱ ላይ ለአካል ጉደተኞች የተመቸ መኾኑንም ተናግረዋል። “መብቴን ተጠቅሜ መምረጤ ለሀገሬ ያለኝን ፍቅር ማሣያ ነው” ብለዋል
ዘጋቢ:- ደስታ ካሣ
የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!
👇👇👇
ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!
Previous articleበምስራቅ ጎጃም ዞን በደብረ ኤልያስ ምርጫ ክልል ለ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ፤ መራጮች በተለያዩ የምርጫ ጣቢያዎች በነቂስ ወጥተው ድምጻቸውን እየሰጡ ነው።
Next articleምርጫውን አፍሪካውያን መታዘባቸው ኢትዮጵያ የፓን አፍሪካኒዝም ፈር ቀዳጅነቷን ዳግም በዴሞክራሲያዊ ምርጫ የደገመችበት ነው።