
የ87 ዓመት የዕድሜ ባለጸጋ አቶ አሊ ሙሳ እንዳሉት በነጻነት በካርዳቸው የሚፈልጉትን መርጠዋል። ምርጫውን በጉጉት ሲጠብቁት እንደነበር ገልጸው የሀገር ህልውና የሚረጋገጠው በምርጫ ካርድ ብቻ በመኾኑ ድምፄን ለአመንኩት ሰጥቼያለሁ ብለዋል።
ሌላኛው ድምጽ ሲሰጡ ያገኘናቸው አቶ ግርማ ተሻለ ለሀገር የሚበጀውን እንደመረጡ ገልጸዋል።
የምርጫ ሂደቱ ፍጹም ሰላማዊ፣ ነጻነት ያለው፣ ያለምንም ወከባ የሚፈልጉትን የመረጡበት ስለመኾኑም ጠቁመዋል።
ሌሎች የከተማ ነዋሪዎችም ይጠቅመኛል፣ ይበጀኛል፣ ያስተዳድረኛል ያሉትን በካርዳቸው መምረጣቸውን ለአሚኮ ተናግረዋል።
ዘጋቢ፦አዳሙ ሽባባው
ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!
