
ባሕር ዳር: ግንቦት 24/2018 ዓ.ም (አሚኮ) በባሕርዳር ከተማ ምርጫ ክልል የብልጽግና ፓርቲ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እጩ ተወዳዳሪ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ እና የአማራ ክልል ርእሰ መሥተዳድር እና በባሕርዳር ከተማ የብልጽግና ፓርቲ የክልል ምክር ቤት እጩ ተወዳዳሪ አረጋ ከበደ በባሕርዳር ድምጽ ሰጥተዋል።

ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ እና ርእሰ መሥተዳድሩ ድምጽ የሰጡት በባሕርዳር ከተማ ግሽ ዓባይ በሚገኘው ሕዳሴ የምርጫ ጣቢያ ነው።
ዘጋቢ:- ታርቆ ክንዴ
ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!
