የአማራ ክልል የፍርድ ቤቶች ጥሪ ማዕከል በሙሉ አቅሙ ሥራ ጀመረ።

6
ባሕር ዳር: ግንቦት 18/2018 ዓ.ም (አሚኮ) የአማራ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የተገልጋዮችን ወጭ፣ ጊዜ እና እንግልት የሚቀንሱ ዘመናዊ የዳኝነት አገልግሎት መስጫ መሠረተ ልማቶችን በመገንባት ላይ ይገኛል።
ጠቅላይ ፍርድ ቤቱ እየዘረጋቸው ካሉ ዘመናዊ አሠራሮች መካከል ባለጉዳዮች ፍርድ ቤት በአካል መሄድ ሳይጠበቅባቸው ባሉበት ኾነው አገልግሎት የሚያገኙበት የጥሪ ማዕከል ተጠቃሽ ነው።
ይህም 6152 የጥሪ ማዕከል ሲኾን ከሚሰጣቸው አገልግሎቶች ውስጥ👇
👉 የጠቅላይ ፍርድ ቤት እና በሁሉም ከፍተኛ ፍርድ ቤቶች ቀጠሮ ለማወቅ
👉 በኢ-ፋይሊንግ የተከፈቱ መዝገቦች ያሉበትን ደረጃ ለማወቅ
👉 የተሰጠ ውሳኔን ለማወቅ
👉 የስማርት ችሎት አገልግሎቶችን ለማወቅ እና ለፍርድ ቤቶች አገልግሎት አሰጣጥ መሻሻል የሚያግዙ ጥቆማዎችን እና አስተያይቶችን ለመስጠት ያገለግላል።
ተገልጋዮች ከግንቦት 17/2018 ዓ.ም ጀምሮ ዘወትር በሥራ ሰዓት ወደ 6152 የጥሪ ማዕከል በመደወል የፈለጉትን መረጃ ባሉበት ኾነው ማግኘት እንደሚችሉም ከክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
የአሚኮ ዲጅታል ቤተሰብ ይሁኑ
ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን !
Previous articleተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች ራሳቸውን እንዲያስተዋውቁ የአሚኮ ፍትሐዊነት ምን ድረስ ነበር?
Next articleእንኳን ለ1447ኛው የዒድ አል አድሐ በዓል አደረሰን፣ አደረሳችሁ!