
ጎንደር: ግንቦት 18/2018 ዓ.ም (አሚኮ) ብልጽግና ፓርቲ የድጋፍ ሰልፍ እና የምረጡኝ ቅስቀሳ በአይከል ከተማ አካሂዷል።
በመድረኩ የተገኙት የአማራ ክልል ሴቶች ወጣቶች እና ማኅበራዊ ጉዳይ ቢሮ ኀላፊ ብርቱካን ሲሳይ ብልጽግና ፓርቲ የሴቶችን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በትኩረት እየሠራ መኾኑን አንስተዋል።
ፓርቲው ወጣቶች በኢኮኖሚ እና በዲጂታል ቴክኖሎጂ ብቁ እንዲኾኑ መሥራቱን አንስተው ተግባሩ ቀጣይ መኾኑንም ተናግረዋል።
ብልጽግና ፓርቲ ባለፉት አምስት ዓመታት በኢኮኖሚ፣ በፖለቲካ እና በማኅበራዊ ዘርፍ ስኬት ላይ መድረሱን የማዕከላዊ ጎንደር ዞን አሥተዳዳሪ አወቀ አስፈሬ ገልጸዋል።
ፓርቲው ያለፉት ስኬቶችን መሠረት በማድረግ ለወደፊት ጉዞው በጽናት ከሕዝብ ጋር እንደሚሠራም አስገንዝበዋል።
ብልጽግና የዜጎች የሥራ ባሕል እንዲያድግ ስለመሥራቱ የተናገሩት አቶ አወቀ አስፈሬ ለዚህ ማሳያ ደግሞ የኮሪደር ልማት እንደኾነ ጠቅሰዋል።
ብልጽግና ፓርቲ የሚናገረውን የሚተገብር እና የጀመረውን የሚጨርስ ፓርቲ ስለመኾኑም አብራርተዋል።
ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ሰላማዊ እና ፍትሐዊ ኾኖ እንዲጠናቀቅ ሁሉም ኀላፊነቱን ሊወጣ እንደሚገባም አቶ አወቀ መልዕክት አስተላልፈዋል።
በድጋፍ ሰልፉ ላይ የተሳተፉ የአካባቢው ነዋሪዎች ይወክለናል ያሉትን የፖለቲካ ፓርቲ ለመምረጥ መዘጋጀታቸውንም ተናግረዋል።
ዘጋቢ፦ደስታ ካሣ
#አሚኮ_ዜና #የብልጽግና_ፓርቲ_የድጋፍ_ሰልፍ #ጎንደር_አይከል #አማራ_ክልል #ኢትዮጵያ
የአሚኮ ዲጅታል ቤተሰብ ይሁኑ
https://linktr.ee/Amharamediacorporations
ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን !
