
ቁልፍ ታሪካዊ የምርጫ ንግግራቸው በዓለም ታሪክ ውስጥ የሀገራትን አቅጣጫ የቀየሩ፤ ሕዝብን ያነቃቁ እና ከፍተኛ የፖለቲካ ተጽዕኖ ያሳረፉም ይኖራሉ።
ታዲያ ሀገርን ከጥፋት በመታደግ ወደ ብርሃን ያሻገሩት እነዚያ ንግግሮች ዛሬም ድረስ ምሳሌ ናቸው።
በዚህ ወቅት የነጻነት ታጋዩ ኔልሰን ማንዴላ “ሁላችንም የአንዲት ሀገር ልጆች ነን” የሚል ታሪካዊ የዕርቅ ንግግር በማድረግ ደም መፋሰስን አስቀርተዋል። ምርጫው ሰላማዊ እና ዴሞክራሲያዊ ኾኖ እንዲጠናቀቅም አድርገዋል።
“የማንኛውም ናይጄሪያዊ ሕይወት እኔ ከማገኘው የፖለቲካ ሥልጣን በላይ ዋጋ አለው” በማለት በምርጫው መሸነፋቸውን ለሕዝብ በማረጋገጥ ሊፈጠር የነበረን የእርስ በእርስ ግጭት አስቀርተዋል።
ለአፍሪካ የዴሞክራሲ ልምምድም ትልቅ መሠረት እንደጣሉ ነው የሚነገረው።
እ.አ.አ በ2008 አሜሪካ ባካሄደችው ፕሬዝዳንታዊ ምርጫ በባራክ ኦባማ የተሸነፉት ጆን ማኬይን “ኦባማ የእኔም ፕሬዝዳንት ናቸው” በማለት ሽንፈታቸውን በጸጋ በመቀበል ሰላማዊ የሥልጣን ሽግግር አድርገዋል።
ለሀገሪቱ የዴሞክራሲ ሥርዓት እድገት ከፍተኛ አስተዋፅኦም አበርክተዋል። “ተቃውሞን በጩኸት አትግለጹ፤ ምረጡ” የባራክ ኦባማ የሁሌም ንግግር ነው።
ኦባማ በተለያዬ ጊዜ በአሜሪካ ምርጫ ወቅት ተቃውሟቸውን በጩኸት ለሚገልጹ ዜጎች “አትጩኹ፤ ምረጡ” በማለት እውነተኛ እና ፍሬያማ ለውጥ የሚመጣው በምርጫ ሳጥን ድምጽ በመስጠት ብቻ ነው በማለት ለዓለም አስተምረዋል።
እነዚህን ለማሳያነት ጠቀስን እንጅ በዓለም የምርጫ ታሪክ ከሰው አዕምሮ የማይጠፉ ንግግሮችን ያደረጉ ታዋቂ ሰዎች በርካታ ናቸው። ታሪካዊ ንግግሮቻቸው በወቅቱ ካበረከቱት ፋይዳ ባለፈ አሁንም አስፈላጊ እና አስተማሪ ኾነው ቀጥለዋል።
ኢትዮጵያ ሰባተኛውን ጠቅላላ ምርጫ ለማካሄድ ጥቂት ቀናት ቀርቷታል። ይህ ምርጫ ሰላማዊ እና ዴሞክራሲያዊ ኾኖ እንዲጠናቀቅ ኢትዮጵያዊያን ሁሉ ከተጠቀሱት ባለታሪኮች ትምህርት መውሰድ እንዳለባቸው ይታመናል።
ዘጋቢ፦ አድኖ ማርቆስ
የአሚኮ ዲጅታል ቤተሰብ ይሁኑ
ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን !
