በሰሜን ሜጫ ወረዳ ሲገነቡ የቆዩ የተለያዩ መሠረተ ልማቶች ተመረቁ።

3
ባሕር ዳር: ግንቦት 11/2018 ዓ.ም (አሚኮ) በሰሜን ሜጫ ወረዳ ሲገነቡ የቆዩ የተለያዩ የመሠረተ ልማት ፕሮጀክቶች የምረቃ ኘሮግራም ተካሂዷል።
በወረዳው 48 ኘሮጀክቶች የተገነቡ ሲኾን ለግንባታቸው 53 ሚሊዮን በመንግሥት እና 65 ሚሊዮን ብር ደግሞ በኅብረተሰቡ ተሳትፎ የተገነቡ ናቸው።
ከተገነቡት መሠረተ ልማቶች ውስጥ:-
👉 ጤና ጣቢያ፣ ትምህርት ቤት፣ አዳዲስ መንገዶች ግንባታ እና የነባር መንገዶች ጥገና፣ የአርሶ አደሮች ማሠልጠኛ፣ የእንስሳት ክሊኒክ ግንባታ እና ሌሎችም መሠረተ ልማቶች ናቸው።
በምረቃ ፕሮግራሙ ላይ ክልል እና የዞን መሪዎች፣ የሀገር ሽማግሌዎች እንዲሁም የሀገር መከላከያ ሠራዊት አባላት ተገኝተዋል።
ዘጋቢ፦ ሥራውድንቅ ደሳለው
የአሚኮ ዲጅታል ቤተሰብ ይሁኑ !
ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን !
Previous articleበደቡብ ጎንደር ዞን እና በደብረታቦር ከተማ አሥተዳደር የተገነቡ መሠረተ ልማቶች ለአገልግሎት ክፍት ኾኑ።