
ባሕር ዳር፡ ግንቦት 08/2018 ዓ.ም (አሚኮ) የገላን ጉራ ኢንዱስትሪ ፓርክ ምዕራፍ አንድ ግንባታ ተጠናቆ መመረቅ፤ አስተማማኝ እና ጠንካራ ኢኮኖሚን ለመገንባት በጀመርነው የብልጽግና ጉዞ ተደማሪ እመርታ ነው። በመዲናችን በአጠቃላይ በ93.9 ሄክታር መሬት ላይ ከሚያርፈው የፓርኩ ስፋት ውስጥ የመጀመሪያው ምዕራፍ በ43 ሄክታር መሬት ላይ ተገንብቶ ዛሬ ተመርቋል፤ ይህም ለመካከለኛ እና ከፍተኛ ኢንተርፕራይዞች ምቹ የንግድ ከባቢ ከመፍጠር ባሻገር በሺዎች ለሚቆጠሩ ወጣቶቻችን የሥራ ዕድል ይከፍታል።
ፓርኩ የሀገራችን አምራቾች አቅማቸውን በማጎልበት፣ ምርታማነታቸውን ማሳደግና ተወዳዳሪነታቸውን በመጨመር ለከተማችን፣ ለሀገራችንና ለቀጣናው የሚተርፉበት ታላቅ እድልን ይዟል። በሌላ በኩል ተተኪ ምርቶችን በማምረት በአምራቾችና በሸማቾች መካከል ቀጥተኛና ቀልጣፋ የንግድ ትስስር ሲፈጥር፣ ምርቶችን ደግሞ ለውጭ ገበያ በማቅረብ የሀገራችንን የውጭ ምንዛሬ ለማሳደግ ጉልህ ሚና ይጫወታል።
የአሚኮ ዲጅታል ቤተሰብ ይሁኑ
https://linktr.ee/Amharamediacorporations
ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን !
