
ባሕር ዳር፡ ግንቦት 02/2018 ዓ.ም (አሚኮ) በሰሜን ጎጃም ዞን በደቡብ አቸፈር ወረዳ እና በዱርቤቴ ከተማ የብልፅግና ፓርቲ እጩዎችን የማስተዋወቅ እና የምርጫ ቅስቀሳ እየተካሄደ ነው።
በወረዳውና በከተማው በተለያዩ ቀበሌዎች ነው መርሐ ግብሩ እየተከናወነ ያለው። ቅስቀሳ እና የማስተዋወቅ ሥራው ሕዝቡ በመረጃ ላይ ተመሥርቶ እና የእጩዎችን የአመራር ብቃት እና አገልግሎት በውል ተረድቶ እንዲመርጥ የሚያስችል ነው።
በትክክለኛ መረጃ ላይ ተመስርተው ምርጫውን በማከናወን ለተሻለ ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት የበኩላቸውን ንቁ ተሳትፎ እንደሚያደርጉ የፓርቲው አባላትና ደጋፊዎች ገልጸዋል።
ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!
See less
