ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ.ር) የኢትዮጵያን የአምራች ዘርፍ ለማስፋፋት የሚደረገውን ጥረት የሚያጠናክረውን አራተኛውን ‘ኢትዮጵያ ታምርት’ ኤክስፖ 2018 ዛሬ በይፋ መርቀው ከፍተዋል።

5


‎ኤክስፖው እስካሁን ያሳያቸው እና የተመዘገቡ ዋና ዋና ስኬቶች፦

👉የአምራች ዘርፉ ግብዓት አቅርቦት በዓመት ከ9 ሚሊዮን ወደ 15 ሚሊዮን ቶን አድጓል፤

👉ለአዳዲስ የኢንዱስትሪ ኢንቨስትመንቶች ከ3 ነጥብ 4 ጊጋ ዋት በላይ የኤሌክትሪክ ኃይል ቀርቧል፤

‎👉ለአነስተኛና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞች የሚቀርበው የፋይናንስ አቅርቦት ከ8 ነጥብ 1 ቢሊዮን ወደ 50 ቢሊዮን ብር ያደገ ሲሆን ለከፍተኛ ኢንዱስትሪዎች ደግሞ ከ262 ቢሊዮን ብር በላይ ከፍ ብሏል፤

👉ለዘርፉ ከ2 ነጥብ 28 ቢሊዮን ዶላር በላይ የውጭ ምንዛሬ ተመድቧል፤

👉የፋብሪካዎች የማምረት አቅም ከ47 በመቶ ወደ 67 በመቶ አድጓል፤

‎👉የማምረት አቅምና ዕድገት ከ4 ነጥብ 8 በመቶ ወደ 10 ነጥብ 7 በመቶ ከፍ ያለ ሲሆን፣ በቀጣይም ተጨማሪ ዕድገት ይጠበቃል፤

👉ምርትን በሀገር ውስጥ በመተካት እስከ 4 ነጥብ 85 ቢሊዮን ዶላር ማዳን የተቻለ ሲሆን የወጪ ንግድም ከፍተኛ እድገት እያሳየ ይገኛል፤

‎👉ከ2 ሺህ 800 በላይ ኢንቨስትመንቶችን መሳብ የተቻለ ሲሆን፣ ለ1 ነጥብ 4 ሚሊዮን ዜጎች የሥራ ዕድል ተፈጥሯል።

‎ኤክስፖው ኢንዱስትሪዎችን የሚያስተሳስር፣ ኢንቨስትመንትን የሚስብ፣ በመቶዎች የሚቆጠሩ አምራቾችንና በአሥር ሺዎች የሚቆጠሩ ጎብኝዎችን የሚያገናኝ ቁልፍ ሀገራዊ መድረክ ሆኗል።

‎በአጠቃላይ የኤክስፖው መከፈት የአምራች ዘርፉ ለኢኮኖሚ ዕድገት፣ ለሥራ ዕድል ፈጠራና ለዓለም አቀፍ ተወዳዳሪነት ያለውን ፋይዳ በማጉላት የኢትዮጵያን የኢንዱስትሪ ሽግግር እያፋጠነ መሆኑን ያሳያል።

#PMOEthiopia

የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!
👇👇👇
https://linktr.ee/Amharamediacorporations

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous article“ለሚመጣው ትውልድ ጽኑ፣ በኢንዱስትሪ የበለጸገች እና ራሷን የቻለች ኢትዮጵያን እንገነባለን” ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ.ር)