በክረምቱ የዝውውር መስኮት ሮድሪን ጨምሮ በርናንዶ ሲልቫን እና ቲጂያን ራይንደርስን በክረምቱ የሸኙት ዜጎቹ፣ ሌላኛውን አማካኛቸውን ለመሸኘትም ተቃርበዋል።
የ24 ዓመቱ ስፔናዊው አማካኝ ኒኮ ጎንዛሌዝ ቀጣይ ኢትሀድን ለመሰናበት የተቃረበ ተጫዋች ነው።
ኒውካስትል ዩናይትድ 47 ሚሊዮን ዮሮ በመክፈል ጎንዛሌዝን ለመውሰድ በቃል ደረጃ ከሲቲ ጋር መስማማታቸውን ቢቢሲ አስነብቧል።
ዝውውሩ የሚሳካ ከሆነ ኒኮ ጎንዛሌዝ በክረምቱ ኢትሃድን የሚሰናበት አራተኛው የአማካኝ ስፍራ ተጫዋች ይሆናል።
ታደሰ ሙላት



