ባሕር ዳር: ግንቦት 27/2018 ዓ.ም (አሚኮ) የዓለም አትሌቲክስ የወርቅ ደረጃ በሰጠው በቱርኩ ፊንላንድ በተካሄደው ኮንቲኔንታል ቱር የ2026 የፓቮ ኑርሚ ውድድር አትሌት ዓለምናት ዋለ አሸንፋለች።
በሴቶች 3 ሺህ ሜትር መሰናክል ውድድር አትሌት ዓለምናት ዋለ 9 ደቂቃ 16 ሰከንድ 18 ማይክሮ ሰከንድ በመግባት ነው በአንደኝነት ያሸነፈችው።
በወንዶች 3 ሺህ ሜትር መሰናክል ደግሞ አትሌት አብርሃም ሁለተኛ በመውጣት የብር ሜዳሊያ ማሸነፍ ችሏል።
#አሚኮ_ዜና #ስፖርት_አትሌቲክስ
የአሚኮ ዲጂታል ቤተሰብ ይሁኑ !
https://linktr.ee/Amharamediacorporations
ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን !



