
በደቡብ ጎንደር ዞን ደብረ ታቦር ከተማ ዙሪያ «ዓለምሳጋ» በተባለ ቦታ ሲንቀሳቀሱ የነበሩ 12 የታጣቂ ቡድን አባላት የመንግሥትን የሰላም ጥሪ በመቀበል ለሀገር መከላከያ ሠራዊት የምሥራቅ ዕዝ ኮር እጃቸውን ሰጥተዋል።
በሀገር መከላከያ ሠራዊት የቀጣናው ኮር አዛዥ ኮሎኔል ሰጥየ አራጌ እንዳስታወቁት ታጣቂዎቹ የሰላምን መንገድ እንዲመርጡ የኮር፣ የአድማ መከላከል እና የሌሎች የጸጥታ መዋቅሮች መሪዎች በቅንጅት ሠርተዋል።
ወደ ሰላም ከተመለሱት 12 አባላት መካከል ስምንቱ ከነሙሉ ትጥቃቸው መግባታቸውንም አረጋግጠዋል።
ወደ ሰላም ከተመለሱት አባላት መካከል የቡድኑ የብርጌድ አዛዥ ሰጥአረገው እሸቴ፣ የሻለቃ አዛዥ ስመኘው አረዓያ እና የሻምበል አዛዥ አንሙት ፀጋዬ እንደሚገኙበት ተገልጿል።
ወደ ሰላም የተመለሱት ታጣቂዎች በበኩላቸው «ጫካ መግባት ትርጉም የሌለው፣ ለማን እንደምንታገል እና እንደምንሞት ሳናውቅ የምናደርገው ዓላማ የሌለው ትግል በመኾኑ ተጸጽተን መጥተናል» ብለዋል።
አክለውም የበደሉትን ሕዝብ ለመካስ እና የአካባቢውን ሰላም ለማረጋገጥ የበኩላቸውን ድርሻ እንደሚወጡም ተናግረዋል። ዘገባው የምሥራቅ እዝ ነው
#አሚኮ #ሰላም #አማራ_ክልል #ኢትዮጵያ🇪🇹
#ደብረ_ታቦር #መስከረም_06_2019_ዓ_ም
የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!
