ለአዲሱ ምዕራፍ የተዘረጋው የኢትዮጵያውያን የጋራ ጠረጴዛ

6
🇪🇹
ነገ በአዲስ አበባ አንድ ታላቅ አዳራሽ ውስጥ የሀገር ሽታ፣ የባሕል ውበት፣ አንተ ትብስ አንቺ ትብሽ መባባል እና የኢትዮጵያውያን ኅብረ ቀለማት ደምቀው የሚታዩበት አዲስ ታሪካዊ ምዕራፍ ይጀመራል።
ከሀገሪቱ ልዩ ልዩ ማዕዘናት የተውጣጡ ኢትዮጵያውያን ልዩነቶቻቸውን ከደጅ አውልቀው ያለማንም የውጭ ጣልቃ ገብነት ለጋራ ዕጣ ፈንታቸው በአንድነት ለመምከር ዝግጅታቸውን አጠናቅቀው ዋዜማ ላይ ናቸው።
📌የለውጥ ዋዜማው ኢትዮጵያውያን ልዩነቶቻቸውን ይዘው በአንድ ጠረጴዛ ዙሪያ ለመቀመጥ እየተዘጋጁበት ያለ ታሪካዊ ቀንም ነው። የንጋቱ ብርሃን ምን ያህል ያምራል የሚለው ሰወኛ እሳቤ የሚወሰነው በምክክሩ ሂደት እና በውጤቱ ቢኾንም አሁን ባለው የዋዜማ ድባብ ግን አንድ ዕውነት በጉልህ ይታያል። ይህም ሕዝቡ ሰላምን፣ መደማመጥን እና አዲስ የጋራ ጉዞን አጥብቆ መናፈቅ ነው።
💡 ለረጅም ዘመናት የኢትዮጵያ የፖለቲካ እና የማኅበራዊ ውጥረቶች መፍትሔ ከውጭ ሲጠበቅ ቆይቷል። ዛሬ ግን ያ አካሄድ ተቀይሯል።
እየተንከባለሉ የመጡ የኢትዮጵያ ችግሮች ውሥብሥብ ቢኾኑም ባለቤቶቹ ኢትዮጵያውያን ራሳቸው ካልፈቷቸው ማን መጥቶ ይፈታቸዋል? ፈውሱ ያለው በኢትዮጵያውያን እጅ ላይ ነውና መላ የመፈለግ ሂደት ላይ ናቸው።
እንደ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን መረጃ ከነገ ጀምሮ የሚደረገው ሀገራዊ ምክክርም ብዙ ውጤት ያመጣል ተብሎ ተስፋ ተጥሎበታል። ተስፋው የአንድ ወገን አሸናፊነት ሳይኾን የኢትዮጵያ እና የሕዝቦቿ የጋራ ድል የሚረጋገጥበት፣ ለቀጣዩ ትውልድ የሰላም ውርስ የሚተውበት ታሪካዊ አሻራ ነው።
💬 እርሰዎ ከዚህ ታሪካዊ እና ሀገራዊ ምክክር ምን ውጤት ይጠብቃሉ? የሚሰማዎትን ተስፋ እና የሰላም መልዕክት በአስተያየት መስጫው ላይ ያጋሩን! 👇
✍️ በሮዛ የሻነህ
የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!
Previous articleበምክክር ከግጭት አዙሪት መውጣት እና ጠንካራ ሀገር መገንባት አለብን።