“ሕገወጡ የሕወሃት ቡድን ሀገር የማፍረስ ተልዕኮው በግልጽ እየታዬ ነው” አረጋዊ በርሔ (ዶ.ር)

25
የፌዴራል መንግሥት እና ሕገወጡ የሕወሃት ቡድን በፕሪቶሪያ በደረሱት የሰላም ስምምነት መሰረት የፌዴራሉ መንግስት የገባው ቃል መፈፀሙን የትግራይ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ ሊቀመንበር አረጋዊ በርሔ (ዶ.ር) ለአሚኮ ገልጸዋል።
የኢፌዴሪ መንግሥት ስምምነቱን በማክበር ተቋርጠው የነበሩ የመሠረተ ልማቶችን ወደ ሥራ አስገብቷል።
👉የኤሌክትሪክ፣ የባንክ፣ የትራንስፖርት፣ የሕክምና፣ የትምህርት እና ሌሎችንም አገልግሎቶች ሥራ በማስጀመር ቃሉን ፈጽሟል።
👉በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የፀደቀውን በጀትም በመልቀቅ ወደ ክልሉ ልኳል፣
👉በተደጋጋሚ በሕገወጡ የሕወሃት ቡድን በኩል ስምምነቱን ባለማክበር ተደጋጋሚ ስህተት ቢፈጽምም መንግሥት ሆደሰፊ ኾኖ አሳልፏል።
በዚህም መንግሥት የትግራይን እናቶች ከተደጋጋሚ ለቅሶ ለመታደግ ያለውን ቁርጠኝነት አሳይቷል፣
ሕገወጡ የሕወሃት ቡድን ግን የስምምነት ቃሉን ሳያከብር ሀገርን ለማፍረስ እየሠራ ይገኛል ሲሉ አረጋዊ በርሔ (ዶ.ር) ተናግረዋል።
👉ሕገወጡ ቡድን በጦርነት የደም ጥማቱን ለማርካት ስምምነቱን ዕድሜ ማራዘሚያ አድርጎታልም ነው ያሉት። በዚህም ምክንያት በፕሪቶሪያ ስምምነት ሀገሪቱ አግኝታው የነበረውን እፎይታ ወዲያውኑ አበላሽቶታልም ብለዋል።
ሕገወጡ የሕወሃት ቡድን በፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት የፈረመው የሰላም ፍላጎት ኖሮት ሳይኾን፣ በጦርነቱ የደረሰበትን ሽንፈት እና ኪሳራ ጊዜ ለመግዛት መኾኑን ዓለም በግልጽ አውቆታል ነው ያሉት።
ሕገወጡ የሕወሃት ቡድን ሀገር የማፍረስ ተልዕኮው እንዲቆም በትግራይ እየተካሄደ የሚገኘው እምቢተኝነት ተጠናክሮ ቀጥሏል፣ መንግሥትም ሕገ መንግሥታዊ የሕግ የበላይነትን የማስከበር ኀላፊነቱን እንዲወጣ የትግራይ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ መሥራች እና ሊቀመንበር አረጋዊ በርሄ (ዶ.ር) ጥሪ አቅርበዋል።
ዘጋቢ: ኢብራሂም መሃመድ
የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!
Previous articleከጦርነት ማን አተረፈ? የአማራ ሕዝብ የሰላም ጥሪ