
በአማራ ክልል በየዓመቱ በታላቅ ሕዝባዊ ንቅናቄ የሚከናወነው የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት ዘንድሮ “በጎነት ለሀገር ሉዓላዊነትና ለሕዝብ ተጠቃሚነት” በሚል መሪ መልእክት በላቀ የተቀናጀ ዝግጅትና በልዩ ቁርጠኝነት ወደ ተግባር መገባቱን የክልሉ መንግሥት ኮሙኒኬሽን ቢሮ ኀላፊ አባይ መንግስቴ አስታውቀዋል።
ኃላፊው እንደተናገሩት፤ የበጎ ፈቃድ አገልግሎቱ ቀደም ሲል ከነበረው የወቅታዊና የአጭር ጊዜ ዕርዳታ አቅርቦት ልማዳዊ አሠራር በመውጣት፣ ዜጎች ራሳቸውን ችለው ወደ ምርታማነት እንዲሸጋገሩ የሚያስችል የዘላቂ ኑሮ ማሻሻያ ዕቅድን አንግቦ እየተንቀሳቀሰ ይገኛል።
የዘንድሮው የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት ዋና ዋና ምሰሶዎች፦
ማኅበራዊ አንድነትና የታሪክ አሻራ ጥሪ!
በዘንድሮው መርሃ ግብር የክልሉ ወጣቶች፣ የመንግሥት ሠራተኞች፣ የጸጥታ አካላት፣ የሃይማኖት አባቶች፣ ሀገር በቀል ድርጅቶችና ባለሀብቶች በላቀ ተነሳሽነት እየተሳተፉበት ይገኛል።
ይህ ማኅበራዊ መስተጋብር መንግሥት በጅቶ ለመፈፀም የሚያዳግተውን በቢሊዮን የሚቆጠር በጀት በመጋራት፣ ቀሪ አቅም ወደ ሌሎች መሠረታዊ የልማት ዘርፎች እንዲዞር ትልቅ ዕድል መፍጠሩን አቶ አባይ መንግስቴ አስገንዝበዋል።
”የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት ወቅታዊ ተግባር ብቻ ሳይሆን የክልላችንን ልማትና የብልጽግና ጉዞ የሚያፋጥን ስትራቴጂካዊ የልማት መሣሪያ ነው” ያሉት ኃላፊው፤ እያንዳንዱ ዜጋ የታሪክ አሻራውን ያኖር ዘንድ መላው የክልሉ ማኅበረሰብና የልማት አጋሮች የጀመሩትን ድጋፍና አጋርነት አጠናክረው እንዲቀጥሉ የክልሉ መንግሥት ጥሪ ማስተላለፉን ገልጸዋል።
#ባሕር_ዳር፡ ሐምሌ 01/2018 ዓ.ም
የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!
