የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ጠቅላላ ጉባኤውን እያካሄደ ነው።

0
28
አዲስ አበባ: ሚያዚያ 12/2018 (አሚኮ) የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን 29ኛ ጠቅላላ ጉባኤውን በአዲስ አበባ እያካሄደ ይገኛል።
ለሁለት ቀናት በሚቆየው ጉባኤው ከሚወያይባቸው ጉዳዮች መካከል፦
👉የ28ኛው መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤ ቃለ-ጉባኤን ማፅደቅ፣
👉የ2017 በጀት አመት የዕቅድ አፈፃፀም ሪፖርት ላይ ተወያይቶ ማጽደቅ፣
👉የውጭ ኦዲተርን መሰየም እና የ2017 በጀት ዓመት የውጭ ኦዲት ሪፖርት በማዳመጥ ተወያይቶ ማጽደቅ፣
👉ተቋማዊ አሠራር (ሪፎርም) ሰነድ እና የሰው ኀይል መዋቅራዊ ጥናት ላይ ተወያይቶ ማጽደቅ፤
👉የተሻሻለውን የፌዴሬሽኑ መተዳደሪያ ደንብ አይቶ ማጽደቅ፣
👉 የአምስት ዓመት ስትራቴጂክ እቅድ ላይ ተወያይቶ ማጽደቅ፣
👉የተሻሻለውን የፌዴሬሽኑ የግዥ፣ ፋይናንስ እና ንብረት አሥተዳደር መመሪያን ማጽደቅ ይገኙበታል።
ዘጋቢ፦ ሐናማርያም መስፍን
የአሚኮ ዲጅታል ቤተሰብ ይሁኑ
ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን !

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here