የአዲስ አበባ ከተማ ዋንጫ የንግድ መብት በ45 ሚሊዮን ብር ተሸጠ።

0
6
20ኛው የአዲስ አበባ ከተማ ዋንጫ ከመስከረም 09/2019 ዓ.ም እስከ መስከረም 26/2019 ዓ.ም ይካሄዳል።
‎ስድስት የአዲስ አበባ ከተማ ክለቦች እና ከሁለት ተጋባዥ የክልል ክለቦች በድምሩ ስምንት ክለቦች በዘንድሮው የአዲስ አበባ ከተማ ዋንጫ ተሳታፊ እንደሚኾኑ የአዲስ አበባ እግር ኳስ ፌዴሬሽን በሰጠው መግለጫ ይፋ አድርጓል።
‎ቅዱስ ጊዮርጊስ፣ ኢትዮጵያ ቡና፣ መቻል፣ ኢትዮ ኤሌክትሪክ፣ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና ኢትዮጵያ መድን በውድድሩ ተሳታፊ ክለቦች ናቸው። ጋሞ ጨንታ እና አዳማ ከተማ በተጋባዥነት የሚሳተፉ ይኾናል።
‎የአዲስ አበባ እግርኳስ ፌዴሬሽን እዳስታወቀው ውድድሩን ለማዘመን እና ፌዴሬሽኑን በገቢ ለማጠናከር የውድድሩ ኮሜርሽያል መብት ለሦሥት ዓመታት በሚዘልቅ ውል በ45 ሚሊዮን ብር መሸጡን ገልጿል።
‎ፌዴሬሽኑ ከቫርዳስ/vardas እና ኒዮ/neo/ ጋር በተፈራረመው ስምምነት ነው ውድድሩ ለሦሥት ዓመታት በ45 ሚሊዮን ብር የተሸጠው። ስምምነቱም ከዘንድሮው ውድድር ጀምሮ ተግባራዊ ይኾናል ነው የተባለው።
ዘጋቢ፦ባዘዘው መኮንን
የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here