ባርሴሎና ታዳጊውን ተጫዋች ጄሲ ቢሲውን ለማስፈረም ስምምነት ላይ ደረሰ።

0
113
የስፔን ላሊጋው ሻምፒዮን ባርሴሎና ቤልጄማዊውን ወጣት የክንፍ መስመር ተጫዋች ጄሲ ቢሲውን ለማዛወር ከክለብ ብሩጅ ጋር ከስምምነት ላይ ደርሷል።
ታዋቂዎቹ የስፖርት ጋዜጠኞች ማትዮ ሞሬቶ እና ፋብሪዚዮ እንዳረጋገጡት ከኾነ ተጫዋቹ ወደ ባርሴሎና ለመዘዋወር ሙሉ በሙሉ ስምምነት ላይ ደርሷል።
በቅርቡ ወደ ካታሎኒያ በማምራት የሕክምና ምርመራውን እንደሚያደርግ እና ይፋዊ የውል ስምምነት ፊርማውን እንደሚያስቀምጥ ተነግሯል። ባርሴሎና ለዝውውሩ 10 ሚሊዮን ዩሮ ለክለብ ብሩጅ ይከፍላል።
ወጣቱ የክንፍ መስመር ተጫዋች በቤልጄየሙ ክለብ ብሩጅ የወጣት ቡድን ውስጥ አስደናቂ ብቃቱን በማሳየት የባርሴሎናን የምልመላ ቡድን ትኩረት መሳብ እንደቻለ ነው የተገለጸው።
የካታሎኑ የእግር ኳስ ቡድን ባርሴሎና በሃንሲ ፍሊክ መሪነት ከማላሲያ አካዳሚ ፍሬዎች በተጨማሪ ለረጅም ጊዜ ለቡድኑ ፕሮጀክት የሚኾኑ ወጣት እና ባለ ተሰጥኦ ተጫዋቾችን ለማሠባሠብ ጥረት ላይ ይገኛል። የጄሲ ቢሲው ፊርማም የዚሁ ፕሮጀክት አካል መኾኑ ነው የተገለጸው።
የ18 ዓመቱ ታዳጊ ፊርማውን ካኖረ በኋላ የባርሴሎና ሁለተኛ ቡድን የኾነውን ባርሳ አትሌቲክን እንደሚቀላቀል ያሆ ስፖርት አስነብቧል።
በአድኖ ማርቆስ
የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here