የ2026 የዓለም ዋንጫ በስፔን የበላይነት ፍጻሜውን ሲያገኝ ኬሊያን ምባፔ የወርቅ ጫማውን በ10 ግብ መውሰድ ችሏል።
ተጫዋቹ በዓመቱ ሦሥት የወርቅ ጫማዎችን በመውሰድ የመጀመሪያው ተጫዋች በመኾንም ታሪከ ሠርቷል።
በውድድር ዓመቱ የአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ እና የላሊጋው ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪ ኾኖ የጨረሰው አጥቂው ምባፔ የዓለም ዋንጫን የከፍተኛ ግብ አስቆጣሪ የወርቅ ጫማም በመውሰድ ሌላ ታሪክ መሥራት ችሏል፡፡
የ27 ዓመቱ ፈረንሳዊ በ2026 ዓለም ዋንጫ በ10 ግቦች ነው ከፍተኛ ግብ አግቢነቱን ክብር መውሰድ የቻለው።
ይህ ክብር ተጫዋቹን እንዲህ አይነት ታሪክ የሠራ የመጀመርያው ተጫዋች አድርጎታል፡፡
#አሚኮ #ስፖርት
#ባሕር_ዳር #ሐምሌ13_2018 ዓ_ም
የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!



