ባሕር ዳር: ሰኔ 12/2018 ዓ.ም (አሚኮ) በዓለም ላይ ካሉ ተወዳጅ ሊጎች መካከል አንዱ የኾነው የእንግሊዝ ፕሪምየር ሊግ 2026/27 የውድድር ዘመን መርሐ ግብር ይፋ ኾኗል።
የውድድር ዘመኑ ያለፈው ዓመት የእንግሊዝ ፕሪምየር ሊግ የዋንጫ አሸናፊው አርሰናል ከአዲስ አዳጊው ኮቬንትሪ ሲቲ ጋር በሚያደርጉት ጨዋታ ይጀመራል። ቢቢሲ እንደዘገበው የመጀመሪያው ጨዋታ እ.አ.አ, አርብ ነሐሴ 21 ይጀምራል።
ማንችስተር ሲቲ ከበርንማውዝ፣ ሀልሲቲ ከማንችስተር ዩናይትድ፣ ኒውካስትል ከሊቨርፑል በመጀመሪያው ሳምንት ከሚጠበቁ መርሐ ግብሮች መካከል ናቸው።
በያየህ ፈንቴ
ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!



