ሩዋንዳ በዋና ከተማዋ የተወሰኑ አካባቢዎች የ15 ቀናት የእንቅስቃሴ እገዳ አስተላለፈች፡፡
ባሕር ዳር፡ ሰኔ 19/2012 ዓ.ም (አብመድ) የሩዋንዳ መንግሥት የኮሮናቫይረስ ስርጭትን ለመግታት በዋና ከተማዋ ኪጋሊ አንዳንድ አካባቢዎች ከትናንት ምሽት ጀምሮ ለ15 ቀናት የእንቅስቃሴ እገዳ ማስተላለፉን የሀገሪቱ ጤና ሚኒስቴር አስታውቋል፡፡
በዋና ከተማዋ ኪጋሊ በተደረገ አሰሳ በኮሮናቫይረስ የተያዙ...
የሱዳንን ሽግግር ለማገዝ የ1 ነጥብ 8 ቢሊዮን የአሜሪካ ዶላር ከለጋሾች ተገኘ፡፡
ባሕር ዳር፡ ሰኔ 19/2012 ዓ.ም (አብመድ) ሱዳን ሽግግሯን እየፈተነ የሚገኘውን የምጣኔ ሀብት ቀውስ ለመፍታት የሚረዳ የ1 ነጥብ 8 ቢሊዮን የአሜሪካ ዶላር ድጋፍ አግኝታለች፡፡ በጀርመን አዘጋጅነት በተካሄደ ኮንፈረንስ የተሳተፉ ለጋሽ አካላት ናቸው ድጋፉን ያደረጉት፡፡
የአውሮፓ ኅብረት...
ለሕዳሴ ግድብ አፍሪካዊ መፍትሄ እንደሚያስፈልግ ኬንያ ገለጸች።
ባሕር ዳር፡ ሰኔ 18/2012 ዓ.ም (አብመድ) ከሕዳሴ ግድብ ጋር በተያያዘ በኢትዮጵያ፣ በግብፅ እና በሱዳን መካከል ያለው ልዩነት ከፍጥጫ ይልቅ በድርድር ሊፈታ እንደሚገባው ኬንያ አስታውቃለች።
ኬንያ በታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ዙረያ በኢትዮጵያ፣ በግብፅ እና በሱዳን መካከል...
ማዕድን አውጪውን በአንድ ጊዜ ሚሊዬነር ያደረገው አጋጣሚ!
ታንዛንያዊው ማዕድን አውጪ ግለሰብ በአንድ ጊዜ ሚሊዬነር መሆናቸው ተዘግቧል።
የ52 ዓመቱ ግለሰብ በዘርፉ ሥራ ለዓመታት የደከሙ ዝቅተኛ ነዋሪ ናቸው። ከ30 በላይ ልጆች እንዳሏቸውም ቢቢሲ አስነብቧል። “ይታደሉታል እንጂ …” እንዲሉ አንድ ቀን ግን የዘመናት ድካማቸውን ወደ...
የሕዳሴ ግድቡ ለቀጣናው ካለው ፋይዳ አንጻር ጎረቤት ሀገራት ድጋፋቸው ለኢትዮጵያ እንደሚሆን አቶ ገዱ አንዳርጋቸው...
ባሕር ዳር፡ ሰኔ 17/2012 ዓ.ም (አብመድ) ኢትዮጵያ፣ ግብጽና ሱዳን ከግድቡ ጋር በተያያዘ ባደረጓቸው ድርድሮች የግብጽ ወገን የተለያዩ አጀንዳዎችን እያቀረበ ውይይቱን ውጤት አልባ ለማድረግ ተዘጋጅቶ ይመጣ እንደነበር የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ተናግረዋል፡፡
የኢፌዴሪ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ገዱ...








