
የቡሩንዲ ሪፐብሊክ ፕሬዝዳንት ኢቫሪስት ንዴሺሚዬ አዲስ አበባ ገብተዋል።
የቡሩንዲ ሪፐብሊክ ፕሬዝዳንት ኢቫሪስት ንዴሺሚዬ አዲስ አበባ ሲገቡ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ አቀባበል አድርገውላቸዋለ።
ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት የቡሩንዲ ሪፐብሊክ ፕሬዝዳንት ኢቫሪስት ንዴሺሚዬ ወደ ምድረ ቀደምቷ ኢትዮጵያ እንኳን በደሕና መጡ ብለዋል።
በታላቅ የለውጥ ጉዞ ላይ በምትገኘው ኢትዮጵያ የሚኖርዎት ጉብኝትና ቆይታ ስኬታማ እንዲኾን እመኛለሁ ነው ያሉት በመልዕክታቸው።
ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!
