ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ በአምባሳደር ቆንጂት ሥነ ጊዮርጊስ ሕልፈት የተሰማቸውን ሀዘን ገለጹ።

14
ባሕር ዳር: መጋቢት 29/2018 ዓ.ም (አሚኮ) ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ በአምባሳደር ቆንጂት ሥነ ጊዮርጊስ ሕልፈት የተሰማቸውን ሀዘን ገልጸዋል።
ፕሬዝዳንቱ በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት ክብርት አምባሳደር ቆንጂት ሥነ ጊዮርጊስ በማረፋቸው ጥልቅ ሀዘን ተሰምቶኛል ብለዋል።
በዲፕሎማሲው መስክ ለሀገራቸው ኢትዮጵያ እና ለአፍሪካ ላበረከቱት ጉልህ አስተዋጽኦ አስተምህሮ እና ብልህ አመራር ምንጊዜም ይታወሳሉ ነው ያሉት።
ትጉህ እና ከብረት የጠነከሩ ዲፕሎማት ነበሩ ብለዋል በመልዕክታቸው።
የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!
👇👇👇
ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!
Previous articleምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በአምባሳደር ቆንጂት ሥነ ጊዮርጊስ ሕልፈት የተሰማቸውን ሀዘን ገለጹ።
Next article” ፖሊሶቻችን ሀገር እና ሕዝብ የሰጧቸውን አደራ መቼም፣ የትም፣ በምንም ሁኔታ የሚጠብቁ መኾን ይገባቸዋል” ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ