
ባሕር ዳር: መጋቢት 29/2018 ዓ.ም (አሚኮ) ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በአምባሳደር ቆንጂት ሥነ ጊዮርጊስ ሕልፈት የተሰማቸውን ሀዘን ገልጸዋል።
ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት በኢትዮጵያ የዲፕሎማሲ ታሪክ ውስጥ የማይረሳ እና ታላቅ ዐሻራን ማሳረፍ የቻሉት አምባሳደር ቆንጂት ሥነጊዮርጊስ ከዚህ ዓለም በሞት በመለየታቸው ጥልቅ ሐዘን ተሰምቶኛል ብለዋል።
አምባሳደር ቆንጂት እስከ ከፍተኛ ዲፕሎማትነት በደረሰ ረጅም የሥራ ዘመናቸው ለሀገራችን ብሔራዊ ጥቅም ያስመዘገቡት ድል እና ያበረከቱት አስተዋጽዖ ሁልጊዜም በክብር የሚታወስ ነው።
አምባሳደር ቆንጂት ለኢትዮጵያ ዲፕሎማሲ ከነበራቸው አበርክቶ ባለፈ ለሴት ዲፕሎማቶችም የጽናት እና የጥንካሬ ተምሳሌት ነበሩ ነው ያሉት።
ፈጣሪ ነፍሳቸውን በአጸደ ገነት ያኑር፤ ለቤተሰቦቻቸው፣ ለሥራ ባልደረቦቻቸው እና ለወዳጅ ዘመዶቻቸው መጽናናትን እመኛለሁ ብለዋል በመልዕክታቸው።
ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!
