
ባሕር ዳር: መጋቢት23 /2018 ዓ.ም (አሚኮ) የሰው ሠራሽ አስተውሎት (AI) የዕለት ተዕለት ሥራን እያቃለለ ነው። ነገር ግን ከእድገቱ ጋር ተያይዘው የሚመጡ የሳይበር ጥቃቶች አሳሳቢ ኾነዋል።
በቅርቡ በChatGPT የሶፍትዌር ሥርዓት ላይ በተገኘ ከፍተኛ የደህንነት ክፍተት፣ ጥቃት አድራሾች በአንድ “አደገኛና አጥፊ ትእዛዝ” (Malicious Prompt) ብቻ የግልና የተቋማትን መረጃዎች መዝረፍ የሚያስችል አጋጣሚ ተፈጥሮ እንደነበር የቼክ ፖይንት (Check Point) ተመራማሪዎች ይፋ አድርገዋል።
ይህ የደህንነት ስጋት አጥፊ የኾኑ የጽሑፍ ትእዛዞችን በመጠቀም የChatGPTን የመከላከያ አጥር በመጣስ፣ ሚስጥራዊ መረጃዎችን በቀጥታ ወደ ጥቃት ፈጻሚዎች ሰርቨር (Server) ማስተላለፍ ያስችላል።
ይህም ተጠቃሚዎች ወደ ሰው ሠራሽ አስተውሎት የሚጭኗቸውን ልዩ ልዩ ፋይሎች፣ የግል መልእክቶች እና ሚስጥራዊ የድርጅት ሰነዶች ለከፍተኛ አደጋ አጋልጦ ቆይቷል።
ስለዚህ ከማይታወቁ ምንጮች የሚመጡ “አቋራጭ መንገዶችን” ሁልጊዜም በጥርጣሬ መመልከት ይገባል።
የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!
ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!
