
ባሕር ዳር: መጋቢት 13/2018 ዓ.ም (አሚኮ) የተፈጥሮ ገጸ በረከት፣ የሰላምና የውበት ተምሳሌት በሆነችው፣ ታሪክን ከለመለመ ተፈጥሮ ጋር አዛምዶ በያዘው ጣና ሐይቅና በግርማዊው ዓባይ ወንዝ በታጀበችው ውቧ ባሕር ዳር ከተማ ገብተናል።
በባሕር ዳር ደጃዝማች በላይ ዘለቀ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ስንደርስ ደማቅ አቀባበል ላደረጉልን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድርና ለካቢኔያቸው እንዲሁም ለባሕር ዳር ከተማ አስተዳደር አመራሮች ልባዊ ምስጋናዬን አቀርባለሁ።
በምርቃታቸውና በጸሎታቸው ላልተለዩን ክቡራን የሃይማኖት አባቶች፣ የሀገር ሽማግሌዎች እንዲሁም እንግዳን በፈገግታና በፍቅር መቀበል ለጋስ ማንነቱ ለሆነው ለከበረውና ለደጉ የባሕር ዳር ከተማ ሕዝብ ከልብ የመነጨ ምስጋናዬ ይድረሳችሁ።
የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!
👇👇👇
https://linktr.ee/AmharaMediaCorporation
ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!
