
ባሕር ዳር: መጋቢት 07/2018 ዓ.ም (አሚኮ) የሩሲያ ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጋሞ ዞን የተለያዩ ወረዳዎች በደረሰው የመንሬት መንሸራተት አደጋ ሕይወታቸውን ላጡ ወገኖች የተሰማቸውን ሐዘን ገልጸዋል፡፡
ፕሬዚዳንት ፑቲን በጋሞ ዞን በተከሰተው አደጋ ሕይወታቸውን ላጡ ዜጎች የተሰማቸውን ሐዘን ለፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ እና ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ.ር) አስተላልፈዋል፡፡
ፕሬዚዳንቱ ባስተላለፉት የሐዘን መግለጫ መልዕክት በተከሰተው የመሬት መንሸራተት እና የመሬት ናዳ አደጋ ሕይወታቸውን ላጡ ዜጎች ቤተሰቦች እና ወዳጆች መጽናናትን ተመኝተዋል፡፡
በተከሰተው የተፈጥሮ አደጋ ጉዳት የደረሰባቸው ኢትዮጵያውያን በፍጥነት እንዲያገግሙም መልካም ምኞታቸውን ማስተላለፋቸውን በኢትዮጵያ ከሩሲያ ኢምባሲ የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!
