
አዲስ አበባ፡ መጋቢት 05/2018 ዓ.ም (አሚኮ) የሲዳማ ሕዝብ የዘመን መለወጫ “የፊቼ ጫምባላላ” በዓልን የሚቀበልበት የዋዜማ ምሽት የ”ፊጣራ” ሥርዓት “ሻፌታ” ቀርቦ በሀገር ሽማግሌዎች ተመርቆ በደማቅ ሁኔታ ተከብሯል።
በፊጣራ ሥነ ሥርዓቱ ላይ የሲዳማ ክልል ርእሰ መሥተዳድር ደስታ ሌዳሞን ጨምሮ ከፍተኛ የፌዴራል እና የክልል የመንግሥት የሥራ ኀላፊዎች ተገኝተዋል።
ነገ በማለዳው ደግሞ ሕዝቡ ወደ “ሶሬሳ ጉዱ ማሌ” በመትመም አዲሱን ዓመት የሚቀበልበት በዓል ይጠበቃል።
ዘጋቢ፦ ድልነሳ መንግሥቴ
የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!
👇👇👇
https://linktr.ee/AmharaMediaCorporation
ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!
