
ባሕር ዳር፡ መጋቢት 05/2018 ዓ.ም (አሚኮ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ.ር) በጋሞ ዞን ጋጮ ባባ እና ሌሎች ወረዳዎች ተገኝተው ተጎጅዎችን እያጽናኑ ነው።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ባጋሩት መልእክትም በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጋሞ ዞን ጋጮ ባባ እና ሌሎች ወረዳዎች በበልግ ዝናብ ምክንያት በተከሠተው ድንገተኛ የመሬት መንሸራተት አደጋ ሕይወታቸው ላለፈ ዜጎቻችን የተሰማኝን ኀዘን እገልጻለሁ ብለዋል። “መንግሥት ለተጎጂ ወገኖቻችን አስፈላጊውን ድጋፍ ማድረጉን ይቀጥላል” ሲሉም አረጋግጠዋል።
ችግሩን በዘላቂነት ለመፍታት እንዲቻል ተገቢው ጥናትና ሥራ መከናወን አለበት፤ የጥንቃቄ ተግባራትም አስፈላጊዎች ናቸው ብለዋል።
የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!
👇👇👇
https://linktr.ee/AmharaMediaCorporation
ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!
