
ባሕር ዳር: የካቲት 30/2018 ዓ.ም (አሚኮ) የቴሌግራም አካውንት በጠላፊዎች እንዳይወድቅ የሚደረግ ጥንቃቄ
“የሽልማት ባለቤት ኾነዋል”፣ “አካውንትዎ ሊዘጋ ስለኾነ በዚህ ሊንክ ያረጋግጡ” ወይም “ከቴሌግራም ዋና መሥሪያ ቤት የተላከ መልዕክት” የሚሉ ይዘቶች አብዛኛውን ጊዜ የማጭበርበሪያ ዘዴዎች ናቸው። ማንኛውንም ሊንክ ከመጫንዎ በፊት ምንጩን በትክክል ያረጋግጡ።
አካውንትዎን በሌላ ስልክ ወይም ኮምፒውተር ላይ ተጠቅመው መውጣት (Log out) ረስተው ይሆን? ወይም ሳያውቁት ሌላ ሰው እየተጠቀመበት ይሆን?
ለመፈተሽ፦ Settings > Devices ውስጥ በመግባት የማያውቁት መሳሪያ ካለ Terminate በማድረግ በአስቸኳይ ያስወግዱ።
የስልክ ቁጥርዎ፣ የፕሮፋይል ምስልዎ እና የ”Last Seen” ኹኔታዎ ለማያውቁት ሰው እንዳይታይ ማድረግ፣ ከማኅበራዊ ምህንድስና ጥቃቶች ይጠብቅዎታል።
ምንጭ፦የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አሥተዳደር
ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!
