“ማንነታችን ይከበር አልን እንጅ ከጎረቤቶቻችን ጋር አብረን አንኖርም አላልንም” የወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን ነዋሪዎች

39
ባሕር ዳር፡ የካቲት 26/2018 ዓ.ም (አሚኮ) በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት ወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን ሕዝባዊ ሰላማዊ ሰልፎች እየተካሄዱ ነው። በዞኑ የቆራሪት ከተማ ነዋሪዎችም የመንግሥትን የሰላም ጥሪ የሚደግፍ፣ የህወሃትን ለዳግም ጦርነት ትንኮሳ የሚያወግዝ እና መንግሥት ያወጣውን የምርጫ ውሳኔ የሚደግፍ እና የሚያመሰግን ሰላማዊ ሰልፍ እያካሄዱ ነው።
ሰልፈኞቹ በንቅናቄ በመውጣት ለመንግሥት የሰላም ጥሪ ያላቸውን ጠንካራ ድጋፍ አሳይተዋል። የህወሃትን ዳግም የጦርነት ትንኮሳ በማውገዝ አካባቢያቸው የሰላም እና የልማት ማዕከል እንዲሆን ለሀገር መከላከያ ሠራዊት ያላቸውን ደጀንነት አጠናክረው እንደሚቀጥሉም መልእክታቸውን በአደባባይ አስተላልፈዋል።
ህወሃት የፕሪቶሪያውን የሰላም ስምምነት በመጣስ በተለያዩ የአማራ አካባቢዎች ላይ የዳግም ወረራ እንቅስቃሴ እያደረገ መሆኑንም አውግዘዋል።
👉እኛ ወልቃይት ጠገዴዎች ትናንትም ነገም ዛሬም አማራ ነን
👉ማንነታችን ይከበር አልን እንጅ ጎረቤቶቻችን ጋር አብረን አንኖርም አላልንም
👉የፌዴሬሽን ምክር ቤት፣ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ውክልና እንዲኖረን መወሰኑንም እናመሰግናለን
👉በአማራ ክልል ምክር ቤትም ውክልና እንዲኖረን እንጠይቃለን
👉በኢትዮጵያዊነታችንና በአማራነታችን አንደራደርም፣
👉የመመረጥና የመምረጥ ሕጋዊ መብታችን ይከበረልን
👉በህወሃትና ግብረ አበሮቹ ሴራና ተንኮል ሰላምና ልማታችን አይደናቀፍም
👉የፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነት በተሟላ ሁኔታ ይተግበር እና ሌሎችም መልዕክቶች በሕዝባዊ ሰልፉ ላይ ተስተጋብተዋል።
የቆራሪት ከተማ አሥተዳደር ከንቲባ የሽወንድም አስፋው ህወሃት በሕግ የተቀመጠውን የመምረጥና የመመረጥ መብት ለማደናቀፍ እየሠራ ይገኛል፤ ከዚህ አይነት ሕገወጥ ድርጊት መቆጠብም አለበት ብለዋል። ከምርጫ ጋር በተያያዘ መንግሥት የወሰነው ውሳኔ ለወልቃይት ጠገዴ ሕዝብ ህልውናውን የሚያረጋግጥበት መኾኑን ገልጸው ምስጋናም አቅርበዋል።
“ትግላችን የእውነትና የፍትሕ፤ ራስን የመኾን ነው” ሲሉም ተናግረዋል። ሕዝቡም ነፃነቱን አሳልፎ ላለመስጠት ከሀገር መከላከያ ሠራዊቱ ጎን በመሆን ሰላምና ልማትን ማስቀጠል፣ የመምረጥ መብቱን በመጠቀም ህልውናውን ማረጋገጥ ይገባዋል ነው ያሉት። ምርጫው ሰላማዊና ፍትሐዊ እንዲኾንም እንሠራለን ቤለዋል።
የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!
👇👇👇
ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!
Previous articleሀሰተኛ መረጃን እንዴት እንከላከል?
Next article“አንድ በሚያደርገን ላይ ሥንሠራ ሀገር አንድ ትኾናለች፣ ሰላም ትኾናለች፣ ትበጽጋለች” ርእሰ መሥተዳድር አረጋ ከበደ