
ባሕር ዳር: የካቲት 18/2018 ዓ.ም (አሚኮ) የእስራኤሉ ፕሬዝዳንት አይዛክ ሄርዞግ ለይፋዊ ሥራ ጉብኝት አዲስ አበባ ገብተዋል።
ፕሬዝዳንቱ ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ (ዶ.ር) እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሚኒስትር ድኤታ አምባሳደር ብርሃኑ ፀጋዬ አቀባበል አድርገውላቸዋል።
ፕሬዝዳንቱ በአዲስ አበባ በሚኖራቸው ቆይታ የሁለቱን ሀገራት ግንኙነት በሚያጠናክሩ ጉዳዮች ዙሪያ ከመንግሥት ከፍተኛ የሥራ ኀላፊዎች ጋር ውይይት ያደርጋሉ ተብሎ እንደሚጠበቅ ውጭ ጉዳይ ሚኒቴር በማኅበራዊ ትስስር ገጹ ጠቁሟል።
የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!
👇👇👇
https://linktr.ee/AmharaMediaCorporation
ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!
