
ባሕር ዳር: የካቲት 12/2018 ዓ.ም (አሚኮ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ.ር) የሶርጋ ኢኮ ሎጅን ጎብኝተዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት በሶርጋ ሐይቅ ላይ የሚገኘው የሶርጋ ኢኮ ሎጅ በአሁኑ ወቅት በ14 ሄክታር መሬት ላይ እየተገነባ እንደሚገኝ ገልጸዋል።
የፕሮጀክቱ ሥራ በፍጥነት እየተከናወነ ነው፤ በቅርቡ ይጠናቀቃል ተብሎ ይጠበቃል ነው ያሉት። ከነቀምቴ ከተማ በ6 ኪሎ ሜትሮች ርቀት ላይ ብቻ የሚገኘው የሶርጋ ኢኮ ሎጅ አካባቢውን ከመጠበቅ ባሻገር በኮንስትራክሽን እና በተለያዩ አገልግሎቶች የሥራ እድል እንዲፈጥር ተደርጎ የተቀረጸ መኾኑን አንስተዋል።
ፕሮጀክቱ የአካባቢውን ማኅበረሰብ በመጥቀም በክልሉ ዘላቂ ቱሪዝምን የሚያበረታታ ይኾናል ነው ያሉት በመልዕክታቸው።
የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!
👇👇👇
https://linktr.ee/AmharaMediaCorporation
ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!
