ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ.ር) በኦሮሚያ ክልል በቄለም ወለጋ ዞን ሃዋ ገላን ወረዳ የልማት ሥራዎችን ጎበኙ።

9
ባሕር ዳር: የካቲት 11/2018 ዓ.ም (አሚኮ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ.ር) በኦሮሚያ ክልል በቄለም ወለጋ ዞን ሃዋ ገላን ወረዳ የልማት ሥራዎችን ጎብኝተዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት ‎ዛሬ በቄለም ወለጋ ዞን ሃዋ ገላን ወረዳ በሌማት ትሩፋት መርሐ ግብር የለማ የሙዝ እርሻ ከባቢን ጎብኝቻለሁ ብለዋል።
አርሶአደሮች በፍጹም ጽናት፣ ቅንጅት እና ትብብር አካባቢያቸውን በቀየረ ሥራ በመመልከቴ ደስ ብሎኛል ነው ያሉት። የተመለከትነው የእርሻ ሥራ፤ የአካባቢ መሬትን እና የውኃ ሃብትን በአግባቡ መጠቀም ከተቻለ ትርጉም ያለው ለውጥ ማምጣት እንደሚቻል ማሳያ መኾኑን ገልጸዋል።
ባሕላዊ የመስኖ ዘዴዎችን በመጠቀም እና በቅርብ ያለ ሃብትን በሚገባ ጥቅም ላይ በማዋል ማኅበረሰቡ ውጤታማ እና ተስፋ ሰጪ የግብርና ማዕከል መፍጠር ችሏል ነው ያሉት።
በተለይም የመንገድ መሠረተ ልማት የአርሶአደሮችን ምርት በቀላሉ ወደ ገበያ ለማድረስ የፈጠረውን እድል መመልከት እጅግ የሚያበረታታ መኾኑን ገልጸዋል።
ይኽ እድገት የልማት ጥረቶች ከአካባቢው ማኅበረሰብ ፍላጎት እና አቅም ጋር በቅርበት ሲናበቡ ሊገኝ የሚችለውን ውጤት በግልጽ የሚያሳይ ነው ብለዋል በመልዕክታቸው።
የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!
👇👇👇
ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን
Previous articleጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ.ር) ቄለም ወለጋ ገብተዋል።
Next articleጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ.ር) የቄጦ የመስኖ መሠረተ ልማት ፕሮጀክትን ጎበኙ።