
ባሕርዳር ፡ የካቲት 08/2018 ዓ.ም (አሚኮ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ( ዶ.ር) ከደቡብ ሱዳን ፕሬዝዳንት ሳልቫ ኬር ማያርዲት ጋር ተወያይተዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማኀበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት የአፍሪካ ኅብረት የመሪዎች ጉባዔ ሁለተኛ ቀኑ ላይ በተለያዩ ወሳኝ አጀንዳዎች ውይይታችን እያካሄድን፤ ጎን ለጎን ከደቡብ ሱዳን ፕሬዝዳንት ሳልቫ ኬር ማያርዲት ጋር ተገናኝተን በቀጣናዊ የሰላም እና ፀጥታ ጉዳዮች ላይ ተወያይተናል ብለዋል።
አሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!
ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!
