
ባሕር ዳር: የካቲት 04/2018 ዓ.ም (አሚኮ) የኢቢኤስ ቴሌቭዥን ዋና ሥራ አስፈጻሚ እና መስራች የነበሩት አማን ፍስሃጽዮን ባደረባቸው ህመም በህክምና ሲረዱ ቆይተው ዛሬ የካቲት 4 ቀን 2018 ዓ.ም ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል፡፡
ለኢትዮጵያ ሚዲያ ዕድገት ስኬት የማይተካ ሚና የተጫወቱት አቶ አማን የታላቅ ራዕይ ባለቤትና ብርቱ ሰው እንደነበሩም ኢቢኤስ ባወጣው የሀዘን መግለጫ አስታውቋል።
ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!
