
የዓለም አቀፍ ኮንፈረንስ ተሳታፊ እንግዶች የባሕር ዳር ከተማን የልማት ሥራዎች ጎበኙ።
ባሕር ዳር፡ ጥር 19/2018 ዓ.ም (አሚኮ) “የሕግ የበላይነት እና አማራጭ ያለመግባባት መፍቻ ሥርዓቶች ለዘላቂ ሰላም እና ልማት” በሚል መልእክት በአማራ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት እና ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ትብብር በባሕር ዳር ከተማ በተካሄደው ዓለም አቀፍ ኮንፈረንስ ለመሳተፍ የመጡ የውጭ ሀገር ዜጎች እና ሌሎችም ተሳታፊዎች የከተማዋን የልማት ሥራዎች ጎብኝተዋል።
እንግዶች የባሕር ዳር ዓለም አቀፍ ስታዲየም፣ አዲሱ የዓባይ ድልድይ፣ የባሕር ዳር ሞሰብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት፣ አዲሱ ፕላዛ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን ነው ተዘዋውረው የተመለከቱት።
የውጭ ሀገር የኮንፈረንስ ተሳታፊዎች የከተማዋን የልማት ሥራዎች አድንቀዋል። በተለይም በከተማዋ በምሽት ለእግር ጉዞ የተመቸች፣ አየሯ ተስማሚ ሰላሟ የተጠበቀ፣ ለኑሮ እና ለጉብኝትም የምትመች መኾኗን እንግዶቹ መናገራቸውን ከክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!
👇👇👇
https://linktr.ee/AmharaMediaCorporation
ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!
