‎የከተራ በዓል በባሕርዳር ዓባይ ማዶ እየተከበረ ነው።

5
ባሕር ዳር: ጥር 10/2018 ዓ.ም (አሚኮ) በባሕር ዳር ከተማ በተለምዶ ዓባይ ማዶ በሚባለው አካባቢ የሚገኙ ታቦታት በዓባይ ዳር ወደ ሚገኘው ጥምቀተ ባሕር እየወረዱ ነው።
‎በጥምቀተ ባህሩ አስራ ሰባት ታቦታት ይወርዳሉ። ‎የየአብያተ ክርስቲያናቱ የሰንበት ተማሪዎች ያሬዳዊ ዝማሬ እየዘመሩ፣ በገና ደርዳሪዎች በበገና ምስጋና እያቀረቡ፣ ቀሳውስት እያመሰገኑ፣ ወጣቶችም በኾታ እያጀቡ ታቦታት ወደ ማደሪያቸው እያቀኑ ነው።
‎ዘጋቢ ፦ ፍሬሕይወት አዘዘው
የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!
👇👇👇
ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን
Previous articleለጠንካራ ፓርቲ ጠንካራ አደረጃጀት ያስፈልጋል።
Next article“እንኳን ለኢየሱስ ክርስቶስ የጥምቀት በዓል አደረሳችሁ፤ አደረሰን” ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ.ር)