
ባሕር ዳር: ጥር 08/2018 ዓ.ም (አሚኮ) በፊልም እና ቲያትር ተዋናይነት፣ በቴሌቪዥን ፕሮግራም አቅራቢነት እና በሌሎች የጥበብ ሥራዎች የሚታወቀው ነጻነት ወርቅነህ ባደረበት ህመም በድንገት ህይወቱ ማለፉ ታውቋል።
ለበርካታ ዓመታት በኢቢኤስ ቴሌቪዥን የሚተላለፈው የቤተሰብ ጨዋታ ፕሮግራም አዘጋጅና አቅራቢ የሆነው ነጻነት ወርቅነህ ባለትዳር እና የሦስት ልጆች አባት እንደነበር ከኢቢኤስ ቴሌቪዥን የተገኘ መረጃ ያሳያል።
ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!
