
ባሕር ዳር: ታኅሣሥ 01/2018 ዓ.ም (አሚኮ) የወላይታ ሕዝብ ጥንታዊ ስልጣኔ መገለጫ፣ የበለፀገ ታሪክ እና ከሕዝቡ ማንነት ጋር ስር የሰደደ ትስስር ያለው የወላይታ ብሔር የዘመን መለወጫ በዓል የሆነው “ጊፋታ” በዩኔስኮ (UNESCO) በይፋ በመመዝገቡ የተሰማኝን ልባዊ ደስታ ለመግለጽ እወዳለሁ።
ጊፋታ ከአሮጌው ወደ አዲሱ፣ ከጨለማ ወደ ብርሃን መሸጋገርን የሚያበስር፤ እንዲሁም እርቅ እና ፍቅር የሚሰበክበት ታላቅ እሴት ነው።
“ጊፋታ” በዓለም ቅርስነት መመዝገቡ ለሀገራችን የቱሪዝም ዕድገት ተጨማሪ አቅም ከመፍጠሩም በላይ ድሉ ለመላው የወላይታ ሕዝብ እና ለኢትዮጵያውያን በሙሉ ትልቅ ኩራት ነው::
በድጋሜ እንኳን ደስ አለን!
ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!
