በሆሳዕና ከተማ የምክክር መርሐ ግብር እየተካሄደ ነው።

10
አዲስ አበባ: ኅዳር 28/2018 ዓ.ም (አሚኮ) 20ኛውን የብሔሮች፣ ብሔረሰቦች እና ሕዝቦች ቀን ምክንያት በማድረግ ውቧ ሆሳዕና ከተማ የምክክር ቀን መርሐ ግብርን እያካሄደች ትገኛለች።
ከደቂቃዎች በኋላ በሚጀምረው ሀገራዊ የሲምፖዚየም መድረክ ላይ ለመታደም የፌዴሬሽን ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባዔ አገኘሁ ተሻገር፣ የኢፌዴሪ ሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባዔ ታገሰ ጫፎ፣ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርእሰ መሥተዳድር እንደሻው ጣሰው (ዶ.ር)፣ የክልል ርእሳነ መሥተዳድሮች፣ የክልል ምክር ቤት አፈ ጉባኤዎች፣ የብሔር ብሔረሰቦች እና ሕዝቦች ተወካዮች ተገኝተዋል።
ሲምፖዚየሙ ዴሞክራሲ እና የፌዴራል ሥርዓት አተገባበር በኢትዮጵያ፣ የኢትዮጵያ የምርጫ ሥርዓት፣ የብዝኅነት አሥተዳደር በኢትዮጵያ እንዲሁም የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሕዝቦች የጋራ እሴቶች እና ጸጋዎች በሚሉ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ ምክክር እንደሚደረግ ይጠበቃል።
ዘጋቢ፦ ኢብራሒም ሙሐመድ
የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!
👇👇👇
ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!
Previous articleአራት ዐይናው ብላቴን ጌታ ኅሩይ ወልደሥላሴ
Next article“ሥልጣን በምርጫ ካርድ ብቻ የሚገኝ መኾኑን በልዩ ትኩረት መያዝ ያስፈልጋል” አፈ ጉባዔ አገኘሁ ተሻገር