ርእሰ መሥተዳድር አረጋ ከበደ ከአልሚ ባለሃብቶች ጋር በባሕር ዳር ከተማ እየተወያዩ ነው።

2
ባሕር ዳር: ኅዳር 24/2018 ዓ.ም (አሚኮ) ርእሰ መሥተዳድር አረጋ ከበደ በባሕር ዳር ከተማ ውስጥ ለልዩ ልዩ የሆቴልና ቱሪዝም አገልግሎቶች ቦታ ከወሰዱ ባለሃብቶች ጋር እየተወያዩ ነው።
በውይይቱ ላይ ርእሰ መሥተዳድር አረጋ ከበደ፣ የአማራ ክልል ከተማ እና መሰረተ ልማት ቢሮ ኀላፊ ሞላ መልካሙ (ዶ.ር) የባሕር ዳር ከተማ አሥተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ ጎሹ እንዳላማው እና ሌሎችም የከተማ አሥተዳደሩ መሪዎች እየተሳተፉ ነው።
በባሕር ዳር ከተማ ባለኮከብ ሆቴሎችን በመገንባት የከተማዋን የቱሪዝም አቅም ከፍ እንደሚያደርጉ ታምኖባቸው ቦታ የወሰዱ 43 ባለሃብቶች እና ተወካዮቻቸውም ተገኝተዋል።
ባለሃብቶች መሬት ከወሰዱ በኋላ ሕንጻ ቢገነቡም አገልግሎት ግን መስጠት ያልጀመሩ፣ ሕንጻ ግንባታ ጀምረው ያላጠናቀቁ እና ቦታውን አጥረው ያስቀመጡ ናቸው።
የዛሬው ውይይት ዓላማም የባለሃብቶችን የልማት ተግዳሮቶች በጋራ በመፍታት በሙሉ አቅም ወደ ሥራ ለማስገባት ስለመኾኑ በውይይቱ መግቢያ ላይ ተገልጿል።
ዘጋቢ፦ አሚናዳብ አራጋው
የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!
👇👇👇
ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!
Previous articleየብሔር ብሔረሰቦች እና ሕዝቦች ቀን ክልላዊ የማጠቃለያ መርሐ ግብር በደብረ ብርሃን ከተማ እየተካሄደ ነው።
Next articleየምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ መልዕክት፦