
ባሕር ዳር: ኅዳር 14/2018 ዓ.ም (አሚኮ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ.ር) ከካፍ ፕሬዝዳንት ፓትሪስ ሞትሲፒ (ዶ.ር) ጋር ተወያይተዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ባጋሩት መልዕክት ከካፍ ፕሬዝዳንት ዶክተር ፓትሪስ ሞትሲፒ ጋር በአፍሪካ እግር ኳስ እና ኢትዮጵያ በእድገቱ ስለሚኖራት ሚና ፍሬያማ ውይይት አድርገናል ብለዋል።
ለወጣቶች እድገት፣ የስፖርት መሠረተ ልማት ብሎም የአፍሪካን እግር ኳስ በዓለም መድረክ ለማላቅ ከካፍ ጋር ስለሚኖረን ትብብር ተወያይተናል ነው ያሉት።
ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!
