“ኢትዮጵያ ምድሯ ባለ ሦስት ድርብ ሃብት የያዘ ነው” ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ

7
ባሕር ዳር: ኅዳር 04/2018 ዓ.ም (አሚኮ) ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ 4ኛውን ዓመታዊ የማዕድን እና ቴክኖሎጂ ኤክስፖ (MINTEX Ethiopia 2025) በአዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል አስጀምረዋል።
ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት ኢትዮጵያ ምድሯም ልጆቿም ሃብታሞች ናቸው እስክንባል ድረስ ለአፍታም አንቆምም ብለዋል።
ዛሬ 4ኛውን ዓመታዊ የማዕድን እና ቴክኖሎጂ ኤክስፖ (MINTEX Ethiopia 2025) በአዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል ከፍተናል ነው ያሉት።
ኢትዮጵያ ምድሯ ባለ ሦስት ድርብ ሃብት የያዘ ነው። የከርሰ ምድር ሃብቶች፣ የገጸ ምድር ሃብቶችን እና ልዩ የአየር ንብረትን ታድላለች ብለዋል።
ይህን ድልብ ሃብት ከነበረበት የመረሳት አባዜ በማላቀቅ ለሁለንተናዊ ብልጽግና ማሳኪያ ለመጠቀምና የኢትዮጵያን ዕድገት ለማረጋገጥ ጉዞ ጀምረናል ነው ያሉት።
መንግሥት የሰጠው ልዩ ትኩረትና የወሰዳቸው እርምጃዎች ለዘርፉ መነቃቃት እና ተስፋን በማምጣት በማዕድን ኢንቨስትመንትና ወጪ ንግድ ከፍተኛ እመርታን ፈጥረዋል።
ዓለም አቀፍ ኤክስፖው ባለድርሻ አካላትን፣ ባለሃብቶችን ፣ የቴክኖሎጂ አምራቾችን እና ምሁራንን በማሰባሰብ ያሉንን መልካም ዕድሎች የምናሳይበት እና ተግዳሮቶችን በቅንጅት የምንፈታበት ወሳኝ መድረክ ነው ብለዋል በመልዕክታቸው።
የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!
👇👇👇
ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!
Previous articleየብሔር ብሔረሰቦችን በዓል ለማክበር ወደ አካባቢው የሚመጡ እንግዶችን ለመቀበል ዝግጅት ተደርጓል፡፡
Next articleየብሔር፣ ብሔረሰቦች እና ሕዝቦች ቀን ሰላም፣ አንድነት እና ፍቅር የሚሰበክበት የኢትዮጵያውያን ቀን ነው።