የሰሜን ሸዋ ዞን በኢንዱስትሪ ልማት ማበብ ለኢትዮጵያ የኢኮኖሚ ልማት ግዙፍ ተደማሪ አቅም መኾኑን ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ ተናገሩ።

4
ባሕር ዳር: ኅዳር 2/2018 ዓ.ም (አሚኮ) ዛሬ በሰሜን ሸዋ ዞን የሚገኙትን የአግሮ ፕሮሰሲንግ ፓርክ፤ የሴራሚክ ፋብሪካ እና የፐልፕ የወረቀት ፋብሪካዎችን ተዘዋውረው መመልከታቸውን ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ተናገሩ።
ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ባጋሩት መልዕክት እነዚህ ግዙፍ ፋብሪካዎች በኢንዱስትሪ ዘርፍ የጀመርነው ሀገራዊ ሪፎርም እና ትግበራ ውጤት እየታየበት ለመሆኑ ህያው ምስክሮች ናቸው ብለዋል።
ኢትዮጵያ በልዩ ትኩረት የያዘችው የአምራች ዘርፍ በባህሪው የሃብት ብዜት እና የዘርፎችን ትስስር የሚፈጥር እንደኾነም ተናግረዋል።
በሰሜን ሸዋ ዞን የተመለከትናቸው ፋብሪካዎች አምራች በመሆናቸው አዲስ ሃብትን ወደ ኢኮኖሚው ይደምራሉ ያሉት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በዘርፎች ትስስርም የአንዱ ምርት ለሌላው ግብዓት የሚሆን እና በተለይ በሥራ እድል ፈጠራ እና የውጭ ምንዛሬን በማዳኑ በኩል ትልቅ ሚናን የሚወጡ ናቸው፡፡
ሰላም እና ትጋት ካለ ፋብሪካዎች ለልማት፤ ዜጎች ለለውጥ ሃገርም ወደ ዘላቂ ብልጽግና እንደምትራመድ የሰሜን ሸዋ ዞን ማሳያ ናት፡፡
የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!
👇👇👇
ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን
Previous articleየኢትዮጵያ ንግድ ባንክ “ሲቢኢ በጄ ” የተሰኘ አዲስ የዲጂታል ባንኪንግ አገልግሎት ይፋ አደረገ።
Next article26 ሺህ ሄክታር መሬት በበጋ ስንዴ ልማት እንደሚለማ የሰሜን ወሎ ዞን አስታወቀ።