ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ.ር) በባሌ ተራሮች ብሔራዊ ፓርክ የሀረና ክላስተርን ጎብኝተዋል።

6
ባሕር ዳር: ጥቅምት 09/2018 ዓ.ም (አሚኮ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ.ር) በማኀበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት በባሌ ዞን በነበረን የሁለተኛ ቀን ቆይታ የወልመል ወንዝ የመስኖ ልማት እና ተጠቃሚ አርሶ አደሮች ጉብኝት ባሻገር ወደ ባሌ ተራሮች ብሔራዊ ፓርክ የሀረና ክላስተር በመገኘት ምልከታ አድርገናል ብለዋል።
እነዚህ በግንባታ ላይ በባሌ ተራሮች ብሔራዊ ፓርክ ያሉ ፕሮጀክቶች በሃረና ደን የሪራ ኢኮ ሎጅ፣ ከባቢውን፣ የመመገብያ ስፍራዎችን፣ በእግር እና መኪና መንገዶች የቡና ሱቆችን፣ የምግብ አዳራሾችን እስከ ቱሉ ዲምቱ የከፍታ መወጣጫ ስፍራዎች የሚያካትቱ ናቸው ነው ያሉት።
እነዚህ የልማት ሥራዎች ዘላቂ የቱሪዝም ፕሮጀክቶች የአካባቢ የሥራ ፈጠራ ዕድልን የሚያሰፉ እና የጎብኝዎችን ዕድል የሚያሰፉ በመኾኑ በልዩ ምልከታ የሚታዩ ናቸው ብለዋል በመልዕክታቸው።
የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!
👇👇👇
ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!
Previous articleከሰላም ውጭ ያሉ አማራጮች በሙሉ አውዳሚና አክሳሪ ናቸው።
Next articleየአማራ ክልል የፍትሕ እና ሕግ ኢንስቲትዩት ቦርድ ሁለተኛ መደበኛ ሥብሠባዉን በማካሄድ የተለያዩ ውሳኔዎችን አሳለፈ።