
ባሕር ዳር: መስከረም 16/2018 ዓ.ም (አሚኮ) በክርስትና ሃይማኖት ተከታዮች ዘንድ ዛሬ መስከረም 16 ቀን 2018 ዓ.ም የሚከበረው የመስቀል ደመራ በዓልን ምክንያት በማድረግ በባሕር ዳር ከተማ ለተሸከርካሪ ዝግ የሚኾኑ መንገዶችን የባሕር ዳር ከተማ አስተዳደር ፖሊስ መምሪያ ይፋ አድርጓል፡፡
በመኾኑም የትራፊክ መጨናነቅ እንዳይፈጠር አሽከርካሪዎች ከዚህ በታች የተገለፁት መንገዶች ዝግ መኾናቸውን ተገንዝበው ሌሎች አማራጮችን እንዲጠቀሙ ፖሊስ አሳስቧል፡፡
በዚሁ መሠረት ከቀኑ 7፡ 00 ሰዓት ጀምሮ እስከ በዓሉ ፍፃሜ ድረስ፡-




ኅብረተሰቡም ከፖሊስ የሚሰጠውን መረጃ ተገንዝቦ የትራፊክ ፖሊስ አባላት በሚጠቁሙት አማራጭ መንገዶች እንዲጠቀም እና ለትራፊክ ፖሊስ አባላት ትዕዛዝ አስፈላጊውን ትብብር እንዲያደርግ የባሕር ዳር ከተማ አስተዳደር ፖሊስ መምሪያ ጥሪ ማቅረቡን የአማራ ክልል ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ በማኅበራዊ ትስስር ገጹ አጋርቷል።
ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!