
ባሕር ዳር: ነሐሴ 24/2017 ዓ.ም (አሚኮ) የሁርሶ ኮንቲጀንት ማሰልጠኛ ማዕከል ለ10ኛ ጊዜ ያሰለጠናቸውን ምልምል ወታደሮች እያስመረቀ ነው። ተመራቂዎቹ በቆይታቸው ለውትድርና ሙያ ብቁ የሚያደርጋቸውን ስልጠና በተገቢው ሁኔታ ያጠናቀቁ ናቸው።
በምረቃ ሥነ ሥርዓቱ ላይ የሀገር መከላከያ ሠራዊት አመራሮች እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል። የሁርሶ ኮንቲጀንት ማሰልጠኛ ማዕከል ለሀገር ሉዓላዊነት አስተማማኝ መከታ በመኾን የሚያገለግሉና እያገለገሉ ያሉ ጀግኖችን እያፈራ የሚገኝ ተቋም መኾኑን ኢዜአ ዘግቧል።
ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!